የልደታ አስተዳደር ህንጻ 7ኛ ወለል ቢሮ ቁ 703
+251937113003
የቅሬታ አስተያየት መስጫ
ዓርብ, ህዳር 14, 2016 ዓ.ም
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
ተቋማዊ አደረጃጀት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
ደንብና መመሪያዎች
ማስታወቂያ
የደንበኞች አገልግሎት
አገልግሎቶች
ለመልካም አስተዳደር አስተያየት
የቅሬታ አስተያየት መስጫ
የአገልግሎት እርካታ አስተያየት መስጫ
ለማንኛዉም ጥያቄዎ
የጽ/ቤቱን ሮቦት ይጠይቁ
ሚዲያ
ዜና | News
Online TV
Brochure
መጽሄቶች | Magazines
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ይግቡ
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
መጽሄቶች | Magazine
Online TV
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
Web APP
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ይግቡ
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር መልካም አስተዳደር ቅሬትና አቤቱታ ፅህፈት ቤት የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
ጥር 01/05/18, 2018
ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ ተችሏል:- አቶ አሰፋ ቶላ በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የ6 ወራት የመልካም አስተዳደር ስራዎች እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር አፈፃፀም ተገመገመ፡፡ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አስተዳደሩ በበጀት አመቱ 6 ወራት ያከናወናቸው የመልካም አስተዳደር ችግር አፈታት አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡ መድረኩን የመሩት የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አሰፋ ቶላ ሲሆኑ አብዛኞቹ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ሂደት የተገኘባቸው መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መረባረብ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ መሠረታዊ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በቅንጅት እየፈታን የማህበረሰባችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራን ነው ያሉት አቶ አሰፋ አስተዳደሩ ህገ-ወጥነትንና ብልሹ አሰራርን በመታገል በነዋሪው ዘንድ ፍትሃዊ የሆነ ተጠቃሚነት እንዲኖርም ይሰራል ብለዋል። አቶ አሰፋ አያይዘው ተግባራትን በተቀናጀ ሁኔታ በመፈፀም የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ተጠቃሚነቱን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል። የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ በበኩላቸው በተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር እና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄዎች መነሻ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ያሉበት ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀው ቀሪ ስራዎችን በታቀደላቸው የጊዜ ገደብ መሰረት በማጠናቀቅ መረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይልማ ተረፈ በአፈፃፀም መድረኩ ላይ እንዳሉት በባለፋት 6 ወራት የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመርህ እና በአሰራር በመፍታት የአስተዳደሩን ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ ሰጥቶ የመመለስ መርህ በሚገባ አሳክተናል ብለዋል። የግምገማው ተሳታፊዎች በበኩላችን ቅንጅታችንን አጠናክረን የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በበለጠ ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ተገልጋይ ተኮር በመሆኑ ደስተኞች ነን- ተገልጋዮች
ታህሳስ 24, 2018
በአገልግሎት አሰጣጥ የነበረውን ስብራት እየጠገን የደንበኞችን እርካታ የሚያረጋግጥ ፈጣን ግልፅና ምላሽ ሰጭ አገልግሎት እየሰጠን ነው-ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ የሚገኘው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውጤታማነቱ በተገልጋዮች ዘንድ ምገሳ እየተቸረው ነው። ተገልጋዮች እንደገለፁት በአስተዳደሩ እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ችግር ፈች ነው ብለው አገልግሎት አሰጣጡ ተገልጋይ ተኮር እና የተገልጋይ ፍላጋጎትን የሚያሟላ በመሆኑ ደስተኞች ነን ሲሉ ገልፀዋል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ በተገልጋዮች ዘንድ የቅሬታ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል ብለው አሁን ላይ "በአዲስ ዕይታ የልደታ ከፍታ "በሚል መነሻ በአገልግሎት አሰጣጡ የነበሩ ስብራቶችን ጠግነን እርካታን የሚያረጋግጥ ፈጣን ግልፅና ምላሽ ሰጭ አገልግሎት እየሰጠን ነው በማለት ተናግረዋል። ተገልጋዮቻችን የሚያቀርቡትን ጥያቄ በተቀናጀ መንገድ ምላሽ እየሰጠን የልደታን ከፍታ የማረጋገጥ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ። በየደረጃው የሚሰጠው አገልግሎት አሰጣጥ ምልልስን የሚቀንስ እርካታን የሚያረጋግጥ እንዲሆን ለማስቻል ከምንጊዜውም በላይ በትጋትና በቁርጠኝነት እየሰራን ነው ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ።
ዜና | Oduu | News
የህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር ለቴክኒክ ኮሚቴዎችና ባለሙያዎች በክላስተሩ ቅንጅታዊ አሰራር ማስፈፀሚያ ማንዋል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::
ታህሳስ 27, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በአዲሱ የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራር የማስፈፀሚያ ማንዋል ሠነድ ለህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ ፣ለክላስተር አባል ጽ/ቤቶች፣ ለቴክኒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም ለሠራተኞች ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናው ስለክላስተሩ አደረጃጀት፣ ስለ ክላስተሩ አስተባባሪ ሚና፣ የክላስተር አባል ጽ/ቤቶች ሚና እና ከቴክኒክ ኮሚቴዎች የሚጠበቅ ሃላፊነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በተጨማሪም በክላስተሩ ዕቅድ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት አንስተው ግንዛቤ ለታዳሚው ፈጥረዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በስልጠናው የተሻለ ግንዛቤ መፈጠሩን በመግለፅ የክላስተር አባል ጽ/ቤቶች ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወንጀሎችን፣ የደንብ ጥሰቶችንና ህገ ወጥ ድርጊቶችን በመከላከል የማህበረሰቡን ሰላምና ደህንነት መጠበቅ፤ ለህብረተሠቡ እየተሠሩና እየመጡ ያሉ ለውጦችን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በመግለፅ በዕቅዱ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት ሁሉም ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት የጋራ መግባባት ተፈጥሯል::
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አደረገ።
ታህሳስ 24, 2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የሱፐርቪዥን ቡድን በክ/ከተማው የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎችን ከሪፖርት ባሻገር በተለያዩ ተቋማትና ወረዳዎች ላይ የመስክ ምልከታ እያካሄደ ይገኛል። ሱፐርቪዥኑ ያስፈለገበት አላማ የከተማ እና የክ/ከተማው አስተዳደር ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር የተጣጣመ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዋና ዋና ግቦች ትግበራ እና ያሉበትን ደረጃ በማየት ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል ክፍተቶችን ደግሞ ለመሙላት የሚያስችል መሆኑ የሱፐርቪዥን ቡድኑ አመራሮች ገለፃ አድርገዋል። በምልከታው በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ አጠቃላይ በአመራር ስርዓት እና ውጤታማነት፣ በራስ አቅም የተተገበሩ የልማት ስራዎች፣ አገልግሎት ከማዘመን እና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት በማስፋት ረገድ የተሰሩ ስራዎች በምልከታው የሚረጋገጡ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት የስራ ተሞክሮ እና ልምዱን አካፈለ።
ታህሳስ 15, 2018
በልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት በመገኘት የልምድ ልውውጥ ያደረገው የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ አቻ ጽ/ቤት ሲሆን የጽ/ቤቱ ሀላፊ እና ባለሞያዎች በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል። የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይልማ ተረፈ በልምድ ልውውጡ ላይ እንዳሉት በክ/ከተማው የመልካም አስተዳደር ስራዎች ጉዳይ እንደተቋም ተቀናጅቶ የመፍታት ችግር እንደነበር አስታውሰው በአዲስ መልክ የተዋቀረው የክ/ከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ልዩ ትኩረት ጽ/ቤቱ በተሻለ የአፈፃፀም ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። አቶ ይልማ አያይዘው የአመራሩን የተግባር ስምሪት በማስተካከል፣ ቅንጅታዊ አሰራርን ተቋማዊ እንዲሆን በማስቻል እና ህብረተሰቡን የጉዳዩ ባለቤት በማድረግ በእቅድ የሚመራ የመልካም አስተዳደር ችግር አፈታት ተግባር ተጨባጭ ውጤት ማምጣት ተችሏል ሲሉ ለአቻ ክ/ከተማ ጽ/ቤቱ ልምዳቸውን አካፍለዋል። በቅሬታና አቤቱታ በኩል በየተቋሙና ወረዳዎች የተደራጀውን የቅሬታ ኮሚቴ ከመከታተልና መደገፍ ባሻገር ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎች ለማዳመጥ የህብረተሰቡ ጋር መድረኮችን በማዘጋጀት አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲያዳምጥና የቅሬታውን አግባብነት አይቶ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለውጥ እንደመጣበት አቶ ይልማ አክለው ገለፃ አድርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ በማድረግ በአገልግሎት ቀን ተገልጋዮችን ግልፅ በሆነ አግባብ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት በተገኙበት አገልግሎት ፍትሃዊና የተገልጋይን እርካታ በሚጨምር መልኩ መሰጠቱ ለውጤቱ አበርክቶ እንዳለው ተነስቷል። በልምድ ልውውጡ ላይ ተካፋይ የሆኑት የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ እና ባለሞያዎች እንደገለፁት ከአቀባበል ጀምሮ ለተሰጣቸው ቅንነት የተሞላበት ገለፃ አመስግነው ከክ/ከተማው ያገኙት ልምድ ለቀጣይ ስራቸው እንደ ግብዓት እንደሚጠቀሙበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዜና | Oduu | News
በተቀናጀ አገልግሎት ግልፅና እርካታ የሚፈጥር አገልግሎት እየተሰጠን ይገኛል:- ተገልጋዮች
ታህሳስ 14, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ በአገልግሎት ቀን እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ለኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አስተያየታቸውን የሰጡት ተገልጋዮች እንደተናገሩት የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጡ ምልልስን የሚቀንስ፣ ግልፅና ተደራሽ እንደሆነ ገልፀዋል። ተገልጋዮቹ አክለው እንደገለፁት ከዚህ ቀደም አገልግሎት አሰጣጡ ችግሮች የነበረበት እና ቅሬታ የሚፈጥር እንደነበር አንስተዋል። አገልግሎት አሰጣጡ ምላሽ ሰጭ ነው ያሉት ተገልጋዮቹ በአመራሩና በባለሙያው ዘንድ ቅድሚያ ለተገልጋይ የሚለውን መርህ እርካታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ዜና | Oduu | News
ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዮችን ጥያቄ እንመልሳለን። - ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ
ታህሳስ 11, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የባለ ጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ምልከታ ተደርጓል። የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ፣ ምክትል ስራ አስፈፃሚ እና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አራርሳ ድሪባ እንዲሁም ሌሎች የተቋም ሀላፊዎች በተገኙበት የተገልጋይ ቀንን ምክንያት በማድረግ የተቀናጀ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። ተገልጋዮችን ተቀብለው እያነጋገሩ ያገኝናቸው የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንዳሉት ቀልጣፍና ውጤታማ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዮችን ጥያቄ እየመለስን እንገኛለን ብለዋል። ማገልገል ክብር ነው ያሉት ወ/ሮ ልዕልቲ በተለይ የክፍለ ከተማውን ማህበረሰብ ማገልገል ከክብር በላይ ክብር ነው ብለዋል። በክፍለ ከተማው በባለ ጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እንዲሁም ማህበረሰቡን ለማርካት እና የተገልጋዩን እንግልት ለመቀነስ የሚያስችል የተቋማት የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ዜና | Oduu | News
"አስተዳሩ ጠንካራና ዘላቂ የሆነ ተቋም በመገንባት ተደራሽ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት እየሰጠ ነው" ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ
ህዳር 18, 2018
"እየተሰጠ ያለው ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት አስተዳደሩ ለተቋም ግንባታ የሰጠውን ትኩረት ያሳየ ነው" ተገልጋዮች በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል። የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ ለመመለስ አስችሎናል ብለዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለውም ጠንካራና ዘላቂ ተቋም እየገነባን ፈጣን ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ አገልግሎት እየሰጠን ነው ያሉ ሲሆን በዚህም የማህበረሰቡን ዕርካታ እያረጋገጥን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል። በአስተዳደሩ በየትኛውም ተቋም የሚሰጡ አገልግሎቶች እንግልትን የሚቀንሱ እና በአፈፃፀማቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በምንሰጠው አገልግሎት እርካታ እንዲረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በትኩረት እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል። አገልግሎት አሰጣጣችን ለማህበረሰቡ አዳጊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ፍላጎት ምላሽ እንዲሰጥ ለማድረግ በትኩረት ሰርተናል ብለዋል ወ/ሮ ልዕልቲ ። ከዚህ በፊት በተገልጋዩ ዘንድ ምሬት ይፈጥሩ የነበሩ አሰራሮችን እየፈተሽን የማረም ስራ እያከናወን ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በተገልጋይ ዘንድ ተቀባይነት ያለው አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በየደረጃው እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል። ተገልጋዮች በበኩላቸው በክፍለ ከተማው ፈጣን ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ አገልግሎት እያገኘን ነው ብለው ይህም አስተዳደሩ ለተቋም ግንባታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ያሳየ ነው በማለት ተናግረዋል። ተገልጋዮች አክለውም በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ችግራችን ይደመጣል ለችግራችንም ፈጣን እና ተገቢ ምላሽ ይሰጠናል ብለው ለዚህም አስተዳደሩን እናመሰግናለን ሲሉ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ የኢትዮጲያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዛር ተከፈተ።
ህዳር 16, 2018
በክፍለ ከተማው "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የኢትዮጲያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓልን አስመልክቶ በሜክሲኮ አካባቢ ባዛር ተከፍቷል። ባዛሩን የከፈቱት የልደታ ክ/ከተማ የመልካም አስተዳደርና ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ እንደተናገሩት በባዛሩ የተዘጋጀው ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን አስመልክቶ መሆኑን ገልፀው በባዛሩም ጥራት ያላቸው ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ ቀርበዋል ሲሉ ገልፀዋል። መንግስት የኑሮ ውድነቱን ለማርገብ ከቅዳሜና እሁድ ገብያዎች ባለፈ በተለያዩ ሁነቶች ባዛሮችን እያዘጋጀ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ያሉት አቶ በላይነህ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። ማህበረሰቡ ወደ ባዛሩ በመምጣት የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምትም አቶ በላይነህ ጥሪ አቅርበዋል። የክ/ከተማው ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ ሂሩት በቀለ በበኩላቸው ባዛሩ ለተከታታይ 5 ቀናት እንደሚቆይ ገልፀው ማህበረሰቡ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምትም ጥሪ አስተላልፈዋል። በባዛሩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውንም ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
"ህዝብን ማዳመጥ እና ለህዝብ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ መስጠት ለነገ የምናሻግረው ሳይሆን ዛሬ የምንፈፅመው ተግባር ነው"ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ
ህዳር 14, 2018
በልደታ ክ/ከተማ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ ቀጥሏል። በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋዮችን ሲያስተናግዱ ያገኘናቸው የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአደሩ የህዝብ ጥያቄዎች ሳይቀር ፈጣንና ችግር ፈች ምላሽ እየሰጠን ተጠቃሚነትን እያረጋገጥን ነው ብለው አስተዳደሩ ያደሩ የህዝብ ጥያቄዎችን ከመመለስ ባሻገር የኢንሼቲቭ ስራዎችን በማከናወን የላቀ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ነው ሲሉ ገልፀዋል። የልደታን ከፍታን ለማረጋገጥ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ማሻገር የለብንም ብለን 24/7 እየሰራን እንገኛለን ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ህዝብን ማዳመጥ እና ለህዝብ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ መስጠት ለነገ የምናሻግረው ሳይሆን ዛሬ የምንፈፅመው ጉዳያችን ነው በማለት ተናግረዋል። በየደረጃው ያለ አመራርና ባለሙያ ተግባራትን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ መርሁ አድርጎ እንዲሰራ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠርን ነው ያሉት ወ/ሮ ልዕልቲ በትጋትና በቁርጠኝነት ከሰራን የልደታን ከፍታ በአጠረ ጊዜ እናረጋግጣለን ሲሉ ተናግረዋል። የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ እንደተናገሩት በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ማህበረሰቡ የሚያቀርባቸውን ጥያቄዎች በማያዳግም መልኩ ምላሽ እየሰጠን ነው ብለው በዚህም እርካታን ማረጋገጥ ችለናል ሲሉ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ህዳር 11, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና የተሳለጠ እንዲሆን በስፋት እየሠራ ሲሆን፣ በዚህ ተግባር የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ ረቡዕ እና ዓርብ በአስተዳደሩ በአመራር ደረጃ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ በዛሬውም ዕለት የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እና ሌሎች አመራሮች በቢሮ በመገኘት ለተገልጋዮች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዜና | Oduu | News
"በክፍለ ከተማው እየተሰጠ ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ እየሆነ ነው" ተገልጋዮች።
ህዳር 7, 2018
"ከተገልጋዩ ፍላጎት ጋር የሚመጣጠን አገልግሎት ለመስጠት እየሰራን ነው" ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በልደታ ክ/ከተማ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንደገለፁት በክፍለ ከተማው እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ እየሆነ ነው ብለው ለጠየቅነው አገልግሎት የሚሰጠን ምላሽ ተገቢ እና ምልልስን የሚቀንስ ነው በማለት ገልፀዋል። ተገልጋዮች አክለውም በክ/ከተማው እየተሰጠ ያለው አገልግሎት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መሰረታዊ ለውጥን ያመጣ እና ውጤታማ በመሆኑ ደስተኞች ነን ሲሉ ገልፀዋል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ለማህበረሰቡ የምናቀርበው አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና የዜጎችን እርካታ ማረጋገጥ እንዲችል ለማድረግ በትኩረት እየሰራን እንገኛለን ብለው በዚህም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ባሉ ተቋማት ውጤታማና ችግር ፈች አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በቅንጅት እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል። እርካታን በማረጋገጥ ተገልጋዮች በተቋማቶቻችን ላይ እምነት እንዲያሳድሩ ለማስቻል ከምንጊዜውም በላይ በርብርብ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ወ/ሮ ልዕልቲ። ዋና ስራ አስፈፃሚዋ የተገልጋዮችና የተቋማት ግንኙነት በመተማመንና በውጤታማነት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ሰፋፊ ስራዎችን እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
"በአስተዳደሩ እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በተቋማት ላይ እምነት እንድናሳድር አስችሏል" ተገልጋዮች
ህዳር 5, 2018
"የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ዕርካታን እያረጋገጠ ነው" አስተዳደሩ በልደታ ክ/ከተማ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ችግር ፈች በሆነ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ችግር ፈች ሆኖ ቀጥሏል ብለው አገልግሎት አሰጣጡ አስተዳደሩ የተገልጋዮችን ዕርካታ ለማሳደግ እንዲችልም ትልቅ አቅም ሆኖታል ሲሉ ገልፀዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለውም አገልግሎት አሰጣጣችን ፈጣን ቀልጣፋና ፍትሀዊ ከመሆን ባለፈ የተገልጋዮችን ምልልስ የሚቀንስና ችግር ፈች እንዲሆን ተደርጓል ብለው ለዚህም ተገልጋዮች ምስክርነት እየሰጡ ነው በማለት ተናግረዋል። የክ/ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ድሪባ እንደገለፁት በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ የበርካታ ዜጎች የመልካም አስተዳደር ችግር ምላሽ እንዲያገኝ ተደርጓል ብለው ተግባሩ በተቀናጀ እና በተደራጀ መንገድ ተጠናክሮ ይቀጥላል በማለት ገልፀዋል። አቶ አራርሳ አክለውም የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ችግር ፈች ሆኖ ተጠናክሮ ይቀጥላል በማለት ገልፀዋል። ተገልጋዮች በበኩላቸው በተቀናጀ የአንድ መዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎቻች ፈጣን ምላሽ እያገኙ ነው በዚህም በተቋማት ላይ እምነት እንድናሳድር አስችሎናል ሲሉ ገልፀዋል። ፈጣን ግልፅና ፍትሀዊ አገልግሎት በማግኘታችን ደስተኞች ነን ያሉት ተገልጋዮች ለዚህም አስተዳደሩን አመስግነዋል።
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" "ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር እና የሰራተኛውን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው።"- ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ
ህዳር 8, 2018
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ለሰራተኛውና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ ደረጃቸውን የጠበቁ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ስራ አስጀመረ። በዚህ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ አጠቃላይ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ዘላቂ እና ጠንካራ ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለው ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር እና የሰራተኛውን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። አስተዳደሩ፤ በላቀ ትጋትና ቁርጠኝነት ህዝብን በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ልዕልቲ ሰራተኞች ደግሞ በታማኝነትና በቅንነት ህዝቡን እንዲያገለግሉ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል። የመንግስት ሰራተኞችን የኑሮ ጫናን ለማቃለል በመንግስት በኩል የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በስራው አከባቢ ያለአንዳች እንግልት አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችሉ ሰራተኛው አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች በቅረብ እንዲያገኝ ያስችላል ብለዋል። በዚህ መርሀ ግብር ላይ የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማሳለጥ የሚያስችሉ ደረጃቸውን የጠበቁ ቴክኖሎጅዎችን ስራ ማስጀመሩን ወ/ሮ ልእልቲ አያይዘው ገልፀዋል። በዛሬው ዕለት ደረጃውን የጠበቀ የስፖርት ማዕከል፣ ሱፐር ማርኬት፣ የህፃናት መጫዎቻ ስፍራ፣ የመጀመሪያ ህክምና አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ ቤተ-መጽሃፍት እና ሌሎችንም አገልግሎቶች ስራ አስጀምሯል። በተያያዘ አስተዳደሩ ስታንዳርዱን የጠበቀ የወረፋ ማስጠበቂያ፣ የውስጥና የውጭ ካሜራ መቆጣጠሪያ ሴንተር፣ ዲስፕሌዮች፣ ዲጅታል ዙም ሚቲንግ፣ QR ኮድ ያለው የሰራተኞች ባጅና ሌሎችንም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ተግባር አስገብቷል።
ዜና | Oduu | News
አዲስ አበባ የበለፀገች የለመለመች በማድረግና ፍትሀዊ የሆነ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ
ህዳር 9, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችን ተሳትፎ ተጠቃሚነት ከፍ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ወሆኑ ተገለፀ። የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በመድረኩ እንደተናገሩት በክፍለ ከተማውና በወረዳዎች በራስ አቅም የማህበረሰብ አቀፍ ዴኬር በመስራት ልጃቸውን በተመጣጣኝ የሆነ ምግብና ምቹ አካባቢ በመፍጠር ልጆቻቸው በመያዝ እናቶች ልጆቻቸውን በማስቀመጥ ስራ ሰርተው የተሻለ ገቢ እንዲኖራቸው ለማድረግ ተችሏል። በተለያዩ አካባቢዎች የህፃናት መጫወቻ ቦታዎች በመገንባታ ህፃናት እንዲቦርቁና እንዲጫወቱ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በክፍለ ከተማው ተሰርቷል ብለዋል ለወጣትች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በመገንባታ ወጣቱ በስነ ምግባር እንዲታነፅ ስፖርት በመስራት ንቁና ጤንነቱ የተጠበቀ አምራች ሀይል እንዲሆን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ ገልፀዋል ወ/ሮ ልዕልቲ አያይዘው እኛ በኛ ይህን ሰርተናል የጎደሉ ነገሮችን በጋራ በመስራት የልደታ ከፍታን ማረጋገጥ ይገባል በማለት ገልፀዋል። ክፍለ ከተማው የፀጥታ ችግር መለየት በጋራ መስራት ይገባል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አያይዘው የብልሹ አሰራርና ሌብነትን አብረን መታገል ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
ማህበረሰብ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አስተዳደሩና ተቋሙ በልዩ ትኩረት በመስራት ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለፀ።
ህዳር 4, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር የቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ለጉለሌ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ልምድ አካፈለ። በጽ/ቤቱ የተሰሩ ለልምድ ተሞክሮ የሚሆኑ ሪፖርት በማቅረብ የተሰሩ ስራዎችና ሰነዶችን ማየት ችለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር የቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ በልምድ ልውውጡ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደተናገሩት በአስተዳደሩ በሚሰጠው አገልግሎቶች ላይ የነበረው ምልልስ ከማህበረሰብ ጋር ውጤታማ የሆነ ውይይት በማድረግና መግባባት ላይ ተደርሶ ምልልሱን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ መቻሉን ገልፀዋል ። የመልካም አሰተዳደር ችግሮችን ከብሎክ ጀምሮ በመለየት በየደረጃው መፍታት መቻሉን የገለፁት አቶ በላይነህ አያይዘው በአስተዳደሩ ምቹ የስራ ቦታ መፍጠርና ተቋሙን በሰው ሀይል ማሟላት መቻሉ ለሚሰጠው አገልግሎት ወሳኝ መሆኑ ገልፀዋል። ተገልጋዮች ወደ አስተዳደሩ ግቢ ለመገልገል ሲመጡ አስተዳደሩን ውብና ለስራ ምቹ ለአገልግሎት ማራኪ የማድረግ ስራዎች መሠራት በቻሉን አቶ በላይነህ ገልፀዋል። በጽ/ቤቱ አዲሱ ቅንጅታዊ አሰራር ወደ ተግባር በማስገባት የተቀላጠፈ የስራ አፈፃፀም እንዲኖር ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ከተቋሟት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አቶ በላይነህ ገልፀዋል። በአስተዳደሩ ከ58 በላይ በራስ አቅም የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት መጀመርና ማስጨረስ ማህበረሰብን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በመጨረሻም ልምድ ልውውጡ ያደረጉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ አቻ ተቋም በጽ/ቤት የተሰሩ ተግባራት የተሻለና የማህበረሰብን ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ነው በማለት የተደረጉ ወይይቶች የተገልጋዮችን እንግልት የቀነሰበት አግባብ የተሻለ ልምድ እንደወሰዱ አንስተዋል።
ዜና | Oduu | News
"በክፍለ ከተማው እየተሰጠ ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ እየሆነ ነው" ተገልጋዮች
ህዳር 6, 2018
"ከተገልጋዩ ፍላጎት ጋር የሚመጣጠን አገልግሎት ለመስጠት እየሰራን ነው" ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በልደታ ክ/ከተማ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንደገለፁት በክፍለ ከተማው እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ እየሆነ ነው ብለው ለጠየቅነው አገልግሎት የሚሰጠን ምላሽ ተገቢ እና ምልልስን የሚቀንስ ነው በማለት ገልፀዋል። ተገልጋዮች አክለውም በክ/ከተማው እየተሰጠ ያለው አገልግሎት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መሰረታዊ ለውጥን ያመጣ እና ውጤታማ በመሆኑ ደስተኞች ነን ሲሉ ገልፀዋል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ለማህበረሰቡ የምናቀርበው አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና የዜጎችን እርካታ ማረጋገጥ እንዲችል ለማድረግ በትኩረት እየሰራን እንገኛለን ብለው በዚህም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ባሉ ተቋማት ውጤታማና ችግር ፈች አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በቅንጅት እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል። እርካታን በማረጋገጥ ተገልጋዮች በተቋማቶቻችን ላይ እምነት እንዲያሳድሩ ለማስቻል ከምንጊዜውም በላይ በርብርብ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ወ/ሮ ልዕልቲ። ዋና ስራ አስፈፃሚዋ የተገልጋዮችና የተቋማት ግንኙነት በመተማመንና በውጤታማነት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ሰፋፊ ስራዎችን እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
"በተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ምልልስን መቀነስ የቻለ ግልፅና ተደራሽ አገልግሎት እየሰጠን ነው"ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ
ጥቅምት 14, 2018
በልደታ ክ/ከተማ እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ለኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት መግለጫ የሰጡት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት አገልግሎት አሰጣጣችን የተገልጋይ ምልልስን የሚቀንስ፣ ግልፅና ተደራሽ እንዲሆን ቀዳሚ አጀንዳችን አድርገን እየሰራን ነው ብለው በዚህም ባለፍት ጊዚያት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ችለናል ሲሉ ገልፀዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለውም አገልግሎት አሰጣጣችን ከቢሮ አልፎ እስከ ብሎክ ተደራሽ የሚሆንበትን ስርዓት ዘርግተናል ብለው በዚህም የበርካታ ነዋሪዎች ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ ችለናል በማለት ተናግረዋል። አገልግሎት አሰጣጣችን ምላሽ ሰጭ እንዲሆን ተደርጓል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በአመራሩና በባለሙያው ዘንድ ቅድሚያ ለተገልጋይ የሚለውን መርህ አስርፀን እርካታን የማሳደግ ስራ እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ያለበት ደረጃ ለመገምገም የሚያስችል ምልከታ ተካሄደ
ጥቅምት 15, 2018
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር "በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" ብሎ በጀመረው ፕሮግራም መሠረት የአገልግሎት አሰጣጡ ያለበትን ደረጃ ለመገምገም በተለያዩ ወረዳዎች የመስክ ምልከታ ተካሂዷል። የክ/ከተማውፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ፣ የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ፣ የመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ በልደታ ከ/ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በወረዳዎች ያለው የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን በምልከታ ማረጋገጥ ተችሏል። ተገልጋዮች በበኩላቸው ፈጣን ፣ግልፅና ችግር ፈች አገልግሎት እያገኘን ነው ሲሉ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ግልፀኝነትን የፈጠረው የተቀናጀ አገልግሎት አሰጣጥ በርካታ ችግራችን እየተፈታ ነው ሲሉ ተገልጋዮች ጨምረው ገልፀዋል። የአገልግለት ዕለትን ለተገልጋይ ብቻ በማዋል የህዝብ እሮሮን ለመቀነስ ብሎም በተገልጋዮች የሚነሱ አንገብጋቢ የሆኑ ጥያቄዎችን በአግባቡ አድምጦ የመመለስ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ዜና | Oduu | News
ውጤታማ ተቋማዊ ቅንጅት የጋራ ግቦችን ለማሳካት እና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀምን ለማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተገለፀ።
ጥቅምት 16, 2018
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች በተገኙበት 'የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ማስፈፀሚያ' ማንዋል ላይ ውይይት ተደረገ። በውይይት መድረኩ ላይ የልደታ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚ እና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አራርሳ ድሪባ እንዳሉት ውጤታማ ተቋማዊ ቅንጅት የጋራ ግቦችን ለማሳካት እና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀምን ለማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ አራርሳ አያይዘው የመንግስት ተቋማት የሚያገናኛቸውን ስትራቴጂክ ጉዳዮች ለማከናወን የሚፈጠር መዋቅራዊ አደረጃጀት በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካል ለተፈፃሚነቱ ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል። በልደታ ክ/ከተማ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትል እና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አሰፋ ቶላ በበኩላቸው እንዳሉት ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ፣ ተሻጋሪ የሆኑ ተግባራትን በጋራ ለማከናወን፣ የተወሳሰቡ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የዜጎች ፍላጎት በማሟላት ውጤታማነታቸውን ለማሻሻል ማስፈፀሚያ ማንዋሉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የአገልግሎት አሰጣጥና የህብረተሰቡን ተሣትፎ በማሻሻል የዜጎች አመኔታ በመንግስት ተቋማት ላይ እንዲጨምር ያደርጋል በማለት አቶ አሰፋ አክለው ገልፀዋል። የማስፈፀሚያ ማንዋል ሰነዱን ያቀረቡት የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ ሲሆኑ የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ የሀብት አጠቃቀምን ውጤታማ ለማድረግ፣ አንድ ወጥ አሰራርን በማዘጋጀት በመንግስት ተቋማት ትብብርን በማጠናከር የህብረተሰቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ በበኩላቸው ይህ ተቋማዊ ቅንጅት አሰራር በርካታ የተወሳሰቡ ችግሮችን እንደሚፈታ አንስተው ለማንዋሉ ተፈፃሚነት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት የ2108 በጀት ዓመት ከብሎክ የተሰበሰበ የመልካም አስተዳደር መነሻ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ አካሄደ።
መስከረም 11, 2018
በመድረኩ የብሎክ አደረጃጀቶችና የሲቪክ ማህበራት ተሳታፊ ሆነዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ እንደገለጹት በ2018 በጀት ዓመት የነዋሪዎችንና የተቋማትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ለተነሱት ችግሮች መልስ ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች እየሰሩ መሆኑን ገልጸው የብሎክ አደረጃጀቶችና ሲቪክ ማህበራት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የተቋማትና የሲቪክ ማህበራት ከመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የገለጹት አቶ በላይነህ በ2017 የመልካም አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ልየታና አፈጻጸም ላይ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት በያዝነው በጀት ዓመት ውጤታማ ልንሆን ይገባል ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት በክፍለ ከተማችን የተነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሁሉንም ወረዳዎችና ተቋማት የዳሰሱ መሆናቸውን በመግለጽ ችግሮቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲፈቱ ኃላፊነታችንን እንወጣለን ብለዋል። በመድረኩ በ2018 በጀት ዓመት 93 የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ወደተግባር መግባቱ ተገልጿል።
ዜና | Oduu | News
በአንድ ማዕከል ለተገልጋዮች የሚሰጠው አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
መስከረም 10, 2018
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የባለጉዳይ ቀንን በማስመልከት እየተሰጠ በሚገኘው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ላይ ምልከታ ባደረገበት ወቅት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ ፣የልደታ ክ/ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ድሪባን ጨምሮ ሌሎች የተቋማት ሀላፊዎች ባለጉዳዮችን ሲያስተናግዱ መመልከት ተችሏል። የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን አግኝቶ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ፈጣን ምላሽ እያገኙበት እንደሚገኝ ገልፀዋል። አስተያየታቸውን የሰጡን ተገልጋዮች እንደገለፁት በተለይም ሁሉም የስራ ሀላፊዎች በአንድ ማዕከል በመገኘት እየሰጡት ያሉት አገልግሎቶች ግልፅነትንና ታማኝነትን የሚፈጥር ላነሷቸው ጥያቄዎች አጥጋቢ ማብራሪያና ምላሽ እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። የክፍለ ከተማው አስተዳደር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ባለጉዳዮችን በአንድ ማእከል እንዲሁም የፅህፈት ቤት ኃላፊዎች በየቢሯቸው በመገኘት እያስተናገዱ ይገኛሉ
ዜና | Oduu | News
የህብረተሰቡን መሠረታዊ ችግሮች ለይቶ ለመፍታት ርብርብ እንደሚደረግ የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
ነሀሴ 29, 2018
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ካቢኔ አባላት የህብረተሰቡ መሠረታዊ ችግሮች ናቸው ተብለው ከክ/ከተማ እስከ ብሎክ በተለዩ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቷል። እነዚህ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሙሉ በመሉ ሲፈቱ የክ/ከተማው ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እቅዱ ያመላክታል። የካቢኔ አባሉቱ ውይይት ከህብረተሰቡ ለሚቀርቡ ቅሬታዎች፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍትሄ የተሰጠበትን አግባብ በመገምገም ለቀጣይ ተግባር አቅጣጫ ማስቀመጥ አላማ ያደረገ ነው። የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መልካም አስተዳደርን በማስፈን፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ፍትሃዊ፣ ግልፀኝነት እና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የህብረተሰቡን ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ተልዕኮው የሆነው ክ/ከተማው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ ለመፍታት ወደ ተግባር ተገብቷል። ውይይቱን የመሩት የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት በ2018 በጀት ዓመት ማህበረሰቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመለየት ደረጃ በደረጃ እየፈታን እንሄዳለን፤ በበጀት ዓመቱ የማህበረሰቡን ዘላቂ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችንም እናከናውናለን ሲሉ ገልፀዋል። ማህበረሰቡ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ የሚኖረውን ተሳትፎ በተደራጀ መንገድ በመምራት ችግሮችን በዘላቂነት መቅረፍ ያስፈልጋል ያሉት ወ/ሮ ልዕልቲ ለህዝብ ተጠቃሚነት ያለመታከት ሌት ከቀን እንሰራለንም ብለዋል። አቶ አራርሳ ድሪባ የልደታ ክ/ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ በየደረጃው ያለ አመራር የመሪነት ሚናውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል ሲሉ ገልፀዋል። የህዝብ ጥያቄዎችን በተቀናጀ መንገድ እየመለስን መሄድ ይኖርብናል ያሉት አቶ አራርሳ በምንሰራቸው ተግባራት ሁሉ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል። የሌብነት አስተሳሰብና ተግባርን በተጀመረው አግባብ እየታገሉ የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባም ተገልጿል።
ዜና | Oduu | News
በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ!! የባለጉዳይ ቀን በልደታ ክ/ከተማ።
ነሀሴ 28, 2018
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻልና ውጤታማ ለማድረግ "የባለጉዳይ ቀንን ለባለጉዳይ" በሚል አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት እና የፐብሊክ ሰርቪስ ጽ/ቤት በጋራ ባካሄዱት ምልከታ በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በአንድ ማዕከል ተገልጋዮች እየተስተናገዱ ይገኛሉ፡፡ በተመሳሳይ ሌሎች አመራሮችም በቢሯቸው ተገኝተው ተገልጋዮችን እያስተናገዱ ሲሆን ተቋማትን በመመልከት እንዲሁም በጋራ ሊመጣ የሚችለውን ስኬታማ አገልግሎት ለማሳደግ የሚደረገው የክትትልና ሱፐርቪዥን ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ፡፡
ዜና | Oduu | News
የአንድ ማዕከል አገልግሎት በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ነሀሴ 21, 2018
አስተዳደሩ የአገልግሎት ቀንን ምክንያት በማድረግ በአንድ ማእከል አገልግሎት ነዋሪውን እያገለገለ ይገኛል። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ረቡዕና ዓርብን ማዕከል አድርጎ የተገልጋዮችን ቅሬታ ለመቀነስ የልደታ ክፍለ የቅሬታ እና አቤቱታ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ፥የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ተስፋዬን ጨምሮ የዋና ስራ አስፈፃሚዎች አማካሪዎች በተገኙበት እየተሰጠ ሲሆን የበርካቶች ችግር እየተፈታ እንደሚገኝ የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን በቦታው ተገኝቶ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገልፀዋል። በአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጡም የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች፣ የኮሪደር ልማት ተነሺዎች እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጥ በቂ ምላሽ ያላገኙ ነዋሪዎች ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በአንድ ማእከል አገልግሎቱ አንድ ዓይነት ጉዳይ ያላቸውን በጋራ ምላሽ በመስጠት፣ ወረፋን በመጠበቅ የሚጠፋ ጊዜን በመቆጠብ፣ ብልሹ አሰራርን ለማስወገድና ግልፀኝነትን ለመፍጠር ፣ እንዲሁም በቢሮ ያልተገደበ አገልግሎት በመስጠት አንዱ ለአንዱ ምስክር የሚሆንበትን አሰራርም በመፍጠር የተገልጋዩን ህብረተሰብ አንገብጋቢ ጥያቄዎች ለመመለስ የክፍለ ከተማው አስተዳደር በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ይገኛል።
መግቢያ
ስለ_እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
ፎቶግራፎች | Photo Gallery
ቪዲዮዎች | Videos
መግለጫዎች | Press Release
መጽሄቶች | Magazine
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
Online TV
Web APP
የዛሬይቱ ልደታ
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ያግኙን
lidetaggcg@gmail.com
+251937113003