image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት የ2108 በጀት ዓመት ከብሎክ የተሰበሰበ የመልካም አስተዳደር መነሻ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ አካሄደ።

መስከረም 11, 2017
በመድረኩ የብሎክ አደረጃጀቶችና የሲቪክ ማህበራት ተሳታፊ ሆነዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ መልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ እንደገለጹት በ2018 በጀት ዓመት የነዋሪዎችንና የተቋማትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ለተነሱት ችግሮች መልስ ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች እየሰሩ መሆኑን ገልጸው የብሎክ አደረጃጀቶችና ሲቪክ ማህበራት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የተቋማትና የሲቪክ ማህበራት ከመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የገለጹት አቶ በላይነህ በ2017 የመልካም አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ልየታና አፈጻጸም ላይ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት በያዝነው በጀት ዓመት ውጤታማ ልንሆን ይገባል ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት በክፍለ ከተማችን የተነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሁሉንም ወረዳዎችና ተቋማት የዳሰሱ መሆናቸውን በመግለጽ ችግሮቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲፈቱ ኃላፊነታችንን እንወጣለን ብለዋል። በመድረኩ በ2018 በጀት ዓመት 93 የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ወደተግባር መግባቱ ተገልጿል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች