image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አደረገ።

ታህሳስ 24, 2017
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የሱፐርቪዥን ቡድን በክ/ከተማው የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎችን ከሪፖርት ባሻገር በተለያዩ ተቋማትና ወረዳዎች ላይ የመስክ ምልከታ እያካሄደ ይገኛል። ሱፐርቪዥኑ ያስፈለገበት አላማ የከተማ እና የክ/ከተማው አስተዳደር ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር የተጣጣመ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዋና ዋና ግቦች ትግበራ እና ያሉበትን ደረጃ በማየት ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል ክፍተቶችን ደግሞ ለመሙላት የሚያስችል መሆኑ የሱፐርቪዥን ቡድኑ አመራሮች ገለፃ አድርገዋል። በምልከታው በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ አጠቃላይ በአመራር ስርዓት እና ውጤታማነት፣ በራስ አቅም የተተገበሩ የልማት ስራዎች፣ አገልግሎት ከማዘመን እና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት በማስፋት ረገድ የተሰሩ ስራዎች በምልከታው የሚረጋገጡ መሆኑ ተጠቁሟል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች